የዐቂዳ ክፍል

መልስ - ጌታዬ እኔንም የሚንከባከበኝ እና ዓለማትን ሁሉ በጸጋው የሚንከባከበው የሆነው አላህ ነው።
ማስረጃው ተከታዩ የላቀው አላህ ቃል ነው፦ {ምስጋና ለዓለማት ጌታ ለአላህ የተገባው ነው። 2} [ሱረቱል ፋቲሓ: 2]

ሃይማኖቴ እስልምና ነው። ኢስላም ማለት፦ ለአላህ ብቻ ሁለመናን ሰጥቶ እርሱን በብቸኝነት ማምለክ፣ ለትዕዛዙ ፍፁም ታዛዥ መሆን (መጎተት) እና ከሺርክም ይሁን ከሙሽሪኮች ሙሉ በሙሉ መራቅ (መገለል) ነው።
የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {አላህ ዘንድ የተወደደው ሃይማኖት እስልምና ነው።...} [ኣሊ-ዒምራን፡ 19]

መልስ- ሙሐመድ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ናቸው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ሙሐመድ የአላህ መልክተኛ ናቸው...} [ሱረቱ አል-ፈትሕ፡ 29]

የተውሒድ ቃል የሚባለው "ላኢላሃ ኢላ አላህ" ነው። ትርጉሙም፦ ከአላህ በስተቀር በእውነት ሊመለክ የሚገባው አምላክ የለም ማለት ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {እነሆ ከአላህ በስተቀር እውነተኛ አምላክ አለመኖሩን እወቅ...} [ሱረቱ ሙሐመድ፡ 19]

ሐ - አላህ ሰማይ ላይ ከዓርሹ ከፍ ብሎ ከፍጡራን ሁሉ በላይ ነው ያለው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {(እርሱ) አልረሕማን ነው በዐርሹ ላይ (ለሱ ክብር በሚስማማ መልኩ) ከፍ አለ።} [ሱረቱ ጠሃ፡5] እንዲህም ብሏል፦ {እርሱም ከባሮቹ በላይ ሲሆን አሸናፊ ነው። እርሱም ጥበበኛው ውስጥ ዐዋቂው ነው። 18} [ሱረቱል አል-አንዓም፡ 18]

መልስ - ትርጉሙ፡- አላህ እሳቸውን አብሳሪና አስፈራሪ አድርጎ ለዓለማት የላካቸው መልዕክተኛው መሆናቸውን መመስከር ማለት ነው።
በዚህ ያመነ የሚከተሉት ነገሮች ግዴታ ይሆኑበታል፦
1- ያዘዙትን መታዘዝ፤
2- የተናገሩትን አምኖ መቀበል፤
3- እርሳቸውን አለማመፅ፤
4- እሳቸው በደነገጉት ካልሆነ በቀር አላህ አለማምለክ ነው። ይኸውም ሱናቸውን በመከተል እና ቢድዓን በመተው ነው።
የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {መልክተኛውን የሚታዘዝ ሰው በእርግጥ አላህን ታዘዘ።} (ሱረቱ-አንኒሳእ፡ 80) ጥራት የተገባው አላህ እንዲህም ብሏል፦ {ከልብ ወለድም አይናገርም። እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም። 4} [ሱረቱ-ነጅም 3፡4] ልዕለ ኃያሉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው፣ አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አልላችሁ።21} [ሱረቱል አሕዛብ፡ 21]

መልስ - የፈጠረን ተጋሪ ሳናደርግለት እርሱን ብቻ እንድንገዛው ነው።
ለጨዋታ እና ለዛዛታ አልተፈጠርንም።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ጂኒንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም። (56)} [ሱረቱ-አዝዛሪያት፡ 56]

ሐ -ከንግግርም ይሁን ከተግባር፤ ድብቅም (ውስጣዊ) ይሁን ግልጽ አላህ የሚወደውን ሁሉ የተሰጠ ጥቅል የሆነ ስያሜ ነው።
ግልጽ ሲባል፡- በአንደበት ተስቢሕ (ሱብሐነላህ)፣ ተሕሚድ (አልሐምዱሊላህ)፣ ተክቢራ (አላሁ አክበር) እያደረጉ እና ሶላትና ሐጅን እያከናወኑ አላህን ማውሳት ነው።
ድብቅ (ውስጣዊ) ሲባል፦ ልክ እንደ ተወኩል (በአላህ መመካት) አላህን መፍራትና እና ተስፋን አላህ ላይ ማድረግን ያሉትን ነው።

መልስ - ትልቁ ግዴታችን፡ የላቀው አላህን ብቸኛ አድርጎ ማምለክ ነው።

መልስ-1- ተውሒድ አር-ሩቡቢያህ (የጌትነት አሀዳዊነቱ)፡- አላህ ብቸኛው የሁሉም ፈጣሪ፣ ለጋሽ፣ ባለቤትና ተቆጣጣሪ መሆኑን ማመን ነው።
2- ተውሒድ አል-ኡሉሂያ (የአምልኮ አሀዳዊነቱ)፡- በአምልኮ አላህን ብቻ ነጥሎ ማምለክ ነው። ከላቀው አላህ በስተቀር ማንም በሐቅ የሚመለክ የለም።
3- ተውሒዱል አስማእ ወስሲፋት (በስምና ባህርያቱ ያለው አሀዳዊነት)፡- በቁርአንና በሐዲሥ በተጠቀሱት የአላህ ስም እና ባህሪያቱ ያለ ምንም ምሳሌ መስጠት፣ ከፍጡራንም ጋ ሳያመሳስሉ እና ውድቅም ሳያደርጉ በቁርኣን እና ሱንና በተጠቀሰው መልኩ አምኖ መቀበል ነው።
ለሶስቱ የተውሒድ ዓይነቶች ማስረጃው ተከታዩ የላቀው አላህ ቃል ነው፦ {(እርሱ) የሰማያትና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነውና ተገዛው። እርሱን በመገዛትም ላይ ታገስ። ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን? 65} [ሱረቱ መርየም፡ 65]

መልስ - በልዕለ ኃያሉ አምላካችን አላህ ላይ ሽርክ መፈፀም (ማጋራት) ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም። ከዚህ ሌላ ያለውንም (ኀጢአት) ለሚሻው ሰው ይምራል። በአላህም የሚያጋራ ሰው ታላቅን ኀጢአት በእርግጥ ቀጠፈ።} [ሱረቱ-አንኒሳእ፡ 48]

መልስ- ሽርክ ማለት፦ የትኛውንም አይነት የአምልኮ መገለጫ ከላቀው አላህ ውጭ ላለ አካል አሳልፎ መስጠት ነው።
ዓይነቶቹ፦
ከባዱ ሽርክ ለምሳሌ፡- ከአላህ ውጭ ያለን አካል መማጸን ወይም ከርሱ ውጭ ላለ አካል መስገድ ወይም ከአሸናፊው አላህ ውጭ ላለ አካል እርድ ማቅረብ ነው።
(ትንሹ) መለስተኛው ሽርክ ለምሳሌ፡- ከአላህ ውጭ ባለ አካል መማል፣ ወይም ክታቦችን (ሕርዝ) አልያም መሰል ነገራቶችን ጥቅምን ለማምጣት ወይም ጉዳትን ለመከላከል በሚል እምነት ማንጠልጠል፣ ጥቂትም ቢሆን ሪያእ፣ ማለትም (ለይዩልኝ ብሎ መሥራት) ለምሳሌ ሰዎች እያዩት እንደሆነ አስቦ ሶላትን ማሳመር ይመስል።

መልስ - የሩቅን ምስጢር የሚያውቀው አላህ ብቻ ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {«በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ ሩቅን ምስጢር አያውቅም። ግን አላህ (ያውቀዋል)። መቼ እንደሚቀሰቀሱም አያውቁም» በላቸው። 65} [ሱረቱ-አን'ነምል፡ 65]

መ - 1- በላቀው አላህ ማመን
2 - በመላእክቱ ማመን
3- በመጻሕፍቱ ማመን
4- በመልዕክተኞቹ ማመን
5 - በመጨረሻው ቀን ማመን
6- በቀደር መልካምም ሆነ መጥፎ በሆነ (የአላህ ቅድመ ውሳኔ) ማመን ናቸው።
ማስረጃውም፡- ጂብሪል ዐለይሂ ሰላም ነቢዩን - የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን - ስለ እምነት የጠየቀበት የታወቀው በሙስሊም ዘገባ ውስጥ የሚገኘው ሶሒሕ ሐዲሥ ይገኝበታል፤ በሐዲሡም ጅብሪል ነብዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ስለ ኢማን ሲጠይቃቸው እንዲህ ብለውታል፦ “ስለኢማን ንገረኝ!” አላቸው። እርሳቸውም 'በአላህ፣ በመላእክቶቹ፣ በመጻሕፍቱ ፣ በመልእክተኞቹ፣ በመጨረሻው ቀንና ልታምን እና በቀደር ክፉም ሆነ ደግ ልታምን ነው።' አሉት።"

መልስ - በላቀው አላህ ማመን፡
§ አንተን የፈጠረህ፣ ሲሳይም የሚለግስህ፣ የፍጡራን ሁሉ ባለቤትና ገዥ አላህ መሆኑን ልታምን ነው።
§ በእውነት የሚመለከው እርሱው ነው፤ ከእርሱም ውጭ በእውነት ሊመለክ የሚገባው አምላክ የለም።
§ እርሱ ታላቅና ምሉዕ የሆነና ምስጋናም ሁሉ የተገባው ነው። ለእርሱም ውብ ስሞችና የላቁ ባህሪያት አሉት። ከፍጡራኑም ምንም ዓይነት ብጤም ሆነ አምሳያ የለውም።
በመላእክቶች ማመን፡
መላዕክት አላህ እርሱን እንዲያመልኩት ከብርሀን የፈጠራቸውና ለትእዛዙ ሙሉ በሙሉ ታዛዥ የሆኑ ፍጥረታት ናቸው።
- ከእነርሱ መካከል ጂብሪል ዐለይሂ ሰላም የሚባል አለ፤ ለነብያት ራዕይን ይዞ የሚወርድ ነው።
በመጻሕፍቱ ማመን፡
ይህን ስንል አላህ ወደ መልእክተኞቹ ያወረዳቸው መጻሕፍቶችን ማለታችን ነው።
በነብዩ ሙሐመድ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ላይ የወረደውን ቁርኣን።
በዒሳ የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ላይ በወረደው ኢንጅል።
በሙሳ የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ላይ በወረደው ተውራትን።
በዳውድ የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ላይ በወረደው ዘቡር።
በኢብራሂም እና በሙሳ ዓለይሂማ ሰላም ላይ በወረደው ሱሑፍ።
በመልዕክተኞች ማመን፡
ማለት እነዚያ ባርያዎቹን እንዲያስተምሩ፣ በመልካም እና በጀነት እንዲያበስሩ፣ ከክፉና ከእሳትም እንዲያስጠነቅቁ አላህ ወደ ፍጡራኑ የላካቸው መልዕክተኞች ናቸው።
ከመካከላቸው በላጮቹ፡- ኡሉ-ል-ዓዝም ሲሆኑ እነሱም፡-
ኑሕ የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን
ኢብራሂም የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን
ሙሳ የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን
ዒሳ የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን
ነብዩ ሙሐመድ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ናቸው።
በመጨረሻው ቀን ማመን፡
ይሀውም ሰዎች ከሞቱ በኋላ በመቃብር ውስጥ፣ በቂያማ ቀን፣ ከሞት በሚነሱበትና ፍርዳቸውንም በሚያገኙበት ቀን፣ የጀነት ሰዎች በመኖሪያቸው የጀሀነም ሰዎችም በመኖሪያቸው የሚሰፍሩበት ነው።
በቀደር ክፉውም ሆነ ደጉን ማመን፡
ቀደር፡- አላህ በአጽናፈ ዓለም ውስጥ የሚሆነውን ነገር ሁሉ እንደሚያውቅ፤ ያንንም በጥብቁ ሰሌዳ (በለውሐል መሕፉዝ) ላይ እንዳሰፈረው እና መገኘቱም ሆነ መፈጠሩ በእርሱ መሻት የሚከናወን መሆኑን ማመን ነው።
የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {እኛ ሁሉን ነገር በልክ ፈጠርነው።} [ሱረቱል ቀመር 49]
አራት እርከኖች አሉት፦
የመጀመርያው እርከን፡ ጥራት የተገባው አላህ የሆነውንም የሚሆነውንም ሁሉ አስቀድሞ ጠንቅቆ የሚያውቅ መሆኑ
ማስረጃው ተከታዩ የላቀው አላህ ቃል ነው፦ {አላህ የሰዓቲቱ ዕውቀት እርሱ ዘንድ ብቻ ነው። ዝናብንም ያወርዳል። በማሕፀኖችም ውስጥ ያለን ሁሉ ያውቃል። ማንኛይቱ ነፍስም ነገ የምትሠራውን አታውቅም። ማንኛይቱ ነፍስም በየትኛው ምድር እንደምትሞት አታውቅም። አላህ ዐዋቂ ውስጠ ዐዋቂ ነው። 34} [ሉቅማን፡ 34]
ሁለተኛው እርከን፡- አስቀድሞ የወሰነውንና የፈረደውን ሁሉ በለውሐል መሕፉዝ የመዘገበው መሆኑን ማመን ነው። በመሆኑም የተከሰተውም ይሁን የሚከሰተውም ሁሉ እርሱ ዘንድ ባለው መጽሐፍ ሰፍሯል።
ማስረጃው ተከታዩ የላቀው አላህ ቃል ነው፦ {የሩቅ ነገርም መክፈቻዎች እርሱ ዘንድ ናቸው። ከእርሱ በቀር ማንም አያውቃቸውም። በየብስና በባሕር ያለውንም ሁሉ ያውቃል። ከቅጠልም አንዲትም አትረግፍም የሚያውቃት ቢሆን እንጅ። ከቅንጣትም በመሬት ጨለማዎች ውስጥ የለም ከእርጥብም ከደረቅም አንድም የለም ግልጽ በሆነው መጽሐፍ ውሰጥ (የተመዘገበ) ቢሆን እንጅ። 59} [ሱረቱል አል-አንዓም 59]
ሦስተኛው እርከን፡ ነገራቶችን ሁሉ እውን የሚሆኑት በእርሱ መሻት ነው። በመሆኑም በእርሱ ፈቃድ ካልሆነ በቀር ከእርሱም ሆነ ከፍጥረቱ የሚከሰት ምንም ዓይነት ነገር የለም።
ማስረጃው ተከታዩ የላቀው አላህ ቃል ነው፦ {ከናንተ ቀጥተኛ መሆንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)። 28 የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም። 29} [ሱረቱ-አትተክዊር፡28-29]
አራተኛው እርከን፡- ነገራቶችን ሁሉ የፈጠረው እርሱ መሆኑን ማመን ነው። ራሳቸውን፣ ባህሪያቸው፣ እንቅስቃሴዎቻቸውና በውስጣቸውም ያለውን ሁሉ የፈጠረው እርሱ ነው።
ማስረጃው ተከታዩ የላቀው አላህ ቃል ነው፦ {«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲሆን።» 96} [ሱረቱ-አስሷፍፋት 96]

መልስ - ፍጡር ያልሆነ የኃያሉ አላህ ቃል ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {"ከአጋሪዎችም አንዱ ጥገኝነትን ቢጠይቅ፥ የአላህን ቃል ይሰማ ዘንድ አስጠጋው፤..."} [ሱረቱ አትተውባህ፡ 6]

መልስ - እያንዳንዱ የነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ንግግር፣ ወይ ተግባር፣ ወይም እያወቁ ያጸደቁትን፣ ወይ ተፈጥሯዊ ወይም ባህሪያዊ መገለጫቸውን ሁሉ የሚያጠቃልል ነው።

መልስ - በነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እና በባልደረቦቻቸው ጊዜ ያልነበረ ሰዎች በሃይማኖት ላይ የፈለሰፉት አዲስ ፈሊጥ ሁሉ ቢድዓህ ይባላል።
* ላመጣው ሰው እንመልስለታለን (እናወግዘዋለን) እንጅ አንቀበለውም።
ምክንያቱም ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ስላሉ፡- "ቢድዓ (አዲስ ፈሊጥ) ሁሉ ጥመት ነው።" አቡዳውድ ዘግበውታል።
ለምሳሌ፡- በዒባዳ ላይ መጨመር: ውዱእ ላይ ለአራተኛ ጊዜ ማጠብ እና የነብዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ልደት (መውሊድ) ማክበርን ፤ ይህ ሁሉ ተግባር ከነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ይሁን ከባልደረቦቻቸው የተገኘ ምንም መሰረት የለውም።

መልስ- ወላእ ሲባል፡- ምእመናንን መወዳጀትና መደገፍ ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ምእምንና ምእምናትም ከፊሎቻቸው ለከፊሉ ረዳቶች ናቸው።} [ሱረቱ አትተውባህ፡ 71]
አል በራእ ሲባል ደግሞ፡ ከሓዲያንን የኢስላም ጠላትነታቸውን አውቆ ጠላት አድርጎ መያዝ ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {በኢብራሂምና በእነዚያ ከእርሱ ጋር በነበሩት (ምእምናን) መልካም መከተል አለቻችሁ። ለሕዝቦቻቸው «እኛ ከእናንተ ከአላህ ሌላ ከምትግገዘትም ንጹሖች ነን። በእናንተ ካድን። በአላህ አንድ ብቻ ሲኾን እስከምታምኑ ድረስ በእኛና በእናንተ መካከል ጠብና ጥላቻ ዘወትር ተገለጸ።» ባለ ጊዜ (መልካም መከተል አለቻችሁ)።} [ሱረቱል ሙምተሒናህ፡ 4]

መልስ - አላህ ከእስልምና በስተቀር ሌላ ሃይማኖትን አይቀበልም።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም። እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው። 85} [ሱረቱ ኣሊ-ዒምራን፡ 85]

መልስ - በንግግር ለምሳሌ፡ ጥራት የተገባው አላህን ወይንም መልዕክተኛው የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንን መስደብ።
በተግባር ለምሳሌ፡- ቁርኣንን በተግባር ማቃለል ወይም ከአላህ ውጭ ላለ አካል መስገድን።
በእምነት ለምሳሌ፡- ከኃያሉ አምላክ ሌላ ሊመለክ የሚገባው አካል እንዳለ ወይም ጥራት ይገባውና ከላቀው አምላካችን አላህ ጋ ሌላ አምላክ እንዳለ ማመንን።

መልስ-
1- ከባዱ ኒፋቅ፡- ላይ ላዩን አማኝ መስሎ ክህደትን በውስጥ መደበቅ ነው።
ከእስልምና የሚያስወጣ ሲሆን ከከባዱ የክህደት ዓይነትም ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {መናፍቃን በእርግጥ ከእሳት በታችኛው አዘቅት ውስጥ ናቸው። ለእነሱም ረዳትን አታገኝላቸውም። 145} [ሱረቱ አንኒሳእ፡ 145]
2 - መለስተኛ ሙናፊቅነት:
እንደ መዋሸት፣ ቃል ኪዳንን ማፍረስ እና እምነት መክዳት ያሉት ናቸው።
ከእስልምና የሚያስወጣ ባይሆንም ባለቤቱን ለቅጣት የሚዳርግ ኃጢአት ነው።
የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "የሙናፊቅ ምልክቱ ሶስት ነው፤ ሲናገር ይዋሻል፣ ቃል ሲገባ ቃሉን ያፈርሳል፣ ሲታመን ይክዳል።" ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ - ሙሐመድ ﷺ ናቸው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድም ሰው አባት አይደለም። ግን የአላህ መልክተኛና የነቢዮች መደምደሚያ ነው።...} [ሱረቱል አሕዛብ፡40] የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "እኔ የነብያቶች መደምደሚያ ነኝ፤ ከእኔ በኋላም ነብይ የለም።" አቡዳውድ እና ቲርሚዚይ እንዲሁም ሌሎችም ዘግበውታል።

መልስ- ሙዕጂዛ ማለት፡- ከተፈጥሮና ከተለምዶ ውጪ የሆኑ ለእውነተኝነታቸው ማስረጃ ይሆን ዘንድ አላህ ለነቢያቱ የሰጣቸው ተዓምር ነው።
(ለምሳሌ) ለነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ጨረቃ ለሁለት ተሰንጥቆላቸዋል።
ለሙሳ (ዐለይሂ-ሰላም) ባሕሩን ተከፍሎ አሳልፎ ፈርዖንን እና ጭፍሮቹን ማስጠሙ።

መልስ- ሶሓባ የሚባለው፡- ነብዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን አማኝ ሆኖ አግኝቷቸው በእስልምና ላይ ሆኖ የሞተ ነው።
ሶሓቦችን እንወዳቸዋለንም ፋናቸውንም እንከተላለን፤ እነርሱ ከነብያት በኋላ ከሰዎች ሁሉ በላጭ ናቸው።
ከመካከላቸው በላጮቹ አራቱ ኸሊፋዎች (ቅን ምትኮች) ሲሆኑ እነርሱም፡-
አቡበክር አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው
ዑመር አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው
ዑሥማን አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው
ዐሊይ አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው

መልስ - የነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሚስቶች ናቸው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ነቢዩ በምእምናን ከነፍሶቻቸው ይበልጥ ተገቢ ነው። ሚስቶቹም እናቶቻቸው ናቸው።} [ሱረቱል አሕዛብ፡ 6]

መልስ - ልንወዳቸውና ልንወዳጃቸው እንዲሁም የሚጠላቸውንም ልንጠላ ነው። ይሁን እንጅ በነርሱ ጉዳይ ድንበር አናልፍም። እነርሱም የነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሚስቶችና ዝርያዎች፣ እንዲሁም አማኝ የሆኑት የሀሺም እና የአል-ሙጠሊብ ልጅ ልጆች ናቸው።

መልስ- ግዴታችን፡- አላህንና መልዕክተኛውን እንድናምፅ እስካላዘዙን ድረስ እነርሱን ማክበርና መስማትና መታዘዝ እንዲሁም ለእነርሱ ዱዓእ ማድረግና በድብቅ መምከር ነው።

መልስ- መኖርያቸው ጀነት ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {አላህ እነዚያን ያመኑትንና መልካም ሥራዎችን የሠሩትን በሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች ያገባቸዋል።...} [ሱረቱ ሙሐመድ፡ 12]

መልስ- መኖርያቸው እሳት ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ያችን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ድንጋዮች የሆነችውን እሳት ተጠበቁ፤ ለከሓዲዎች ተደግሳለች። 24} [ሱረቱል በቀራህ፡ 24]

መልስ- አላህን መፍራት ሲባል፡- አላህን እና ቅጣቱን መፍራት ነው።
ተስፋን አላህ ላይ ማድረግ ሲባል ደግሞ፡ የአላህን ምንዳ፣ ይቅር ባይነት እና ምሕረትን ተስፋ ማድረግ ነው።
ማስረጃው ተከታዩ የላቀው አላህ ቃል ነው፦ {እነዚያ እነርሱ የሚግገዟቸው ማንኛቸውም (ወደ አላህ) በጣም ቀራቢያቸው ወደ ጌታቸው መቃረቢያን (ሥራ) ይፈልጋሉ። እዝነቱንም ይከጅላሉ። ቅጣቱንም ይፈራሉ። የጌታህ ቅጣት የሚፈራ ነውና።} [ሱረቱል ኢስራእ፡ 57] የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ባሮቼን እኔ መሓሪው አዛኙ እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው። 49 ቅጣቴም እርሱ አሳማሚ ቅጣት መሆኑን (ንገራቸው)። 50} [ሱረቱል ሒጅር፡ 49-50]

መልስ- አላህ፣ አር-ረብ፣ አር-ረሕማን፣ አስሰሚዕ፣ አል-በሲር፣ አል-ዓሊም፣ አል-ሓይ፣ አል-ዓዚም እና ሌሎችም እጅግ የተዋቡ ስሞችና የላቁ ባሕርያት አሉት።

መልስ- አላህ፡- ትርጉሙም ተጋሪ የሌለው ብቸኛው በእውነት የሚመለክ አምላክ ማለት ነው።
አር-ረብ፡- ትርጉሙም ጥራት የተገባው አምላካችን አላህ ብቸኛው የሁሉም ፈጣሪ፣ ባለቤት፣ ሰጪና አስተናባሪው ማለት ነው።
አስ-ሰሚዕ፡- የመስማት ችሎታው ሁሉንም ነገር የሚያካልል እና በዓይነትም በብዛት የተለያዩ የሆኑ ድምፆችን በሙሉ የሚሰማ ማለት ነው።
አል-በሲር፡ ሁሉንም ነገር የሚያይ እና ትንሹም ይሁን ትልቁን ሁሉ የሚመለከት ነው።
አል-ዓሊም፡ እውቀቱ ያለፈውን፣ የአሁኑንና የወደፊቱን ሁሉ ያካለለ ነው።
አር-ረሕማን፡ እዝነቱ ለእያንዳንዱ ህያው ፍጡር ሁሉ የተዘረጋ ሲሆን ፍጡራን ሁሉ በእዝነቱ ስር ናቸው።
አር-ረዛቅ፡- የሰውም፣ የጂንም እና የተንቀሳቃሽ ህያው ሁሉ ሲሳይ እርሱ ዘንድ የሆነ ነው።
አል-ሓይ፡- የማይሞት ህያው የሆነ ነው። ፍጥረታት ሁሉ ሟች ናቸው።
አል-ዓዚም፡ በስሙም በባህሪያቱም እንዲሁም በድርጊቶቹም ፍጹምነት እና ልዕልና ያለው ነው።

መልስ - እንወዳቸዋለን፤ ሸሪዓዊ ህግጋቶችን እና አጋጣሚዎችን በተመለከተ ከእውቀት አኳያ መመለሻችን እናደርጋቸዋለን፤ በጥሩ ነገር ካልሆነ በስተቀር አናነሳቸውም፤ እነርሱን በመጥፎ የሚያነሳቸውም መንገድ የሳተ እንደሆነ እናምናለን።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {አላህ ከናንተ እነዚያን ያመኑትንና እነዚያንም ዕውቀትን የተሰጡትን በደረጃዎች ከፍ ያደርጋል። አላህም በምትሰሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው። 11} [ሱረቱ አል-ሙጃዲላህ 11]

መልስ- እነርሱ ጥንቁቆቹ (አላህን የሚፈሩ) አማኞች ናቸው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ንቁ! የአላህ ወዳጆች በእነሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም። 62 (እነሱም) እነዚያ ያመኑትና ይፈሩት የነበሩ ናቸው። 63} [ሱረቱ ዩኑስ፡ 62-63]

መልስ- ኢማን ንግግር፣ ተግባርም እምነትም ነው።

መልስ - ኢማን አላህን በመታዘዝ የሚጨምር እና አላህንም በማመፅ የሚቀንስ ነገር ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ፍጹም ምእምናን እነዚያ አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፣ በነሱም ላይ አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ እምነትን የሚጨምሩላቸው፣ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩት ናቸው። 2} [ሱረቱል አንፋል፡ 2]

መልስ - ኢሕሳን ማለት አላህን ልክ እንደምታየው ሆነህ ልታመልከው ነው፤ አንተ ባታየውም እርሱ ያይሀልና።

መልስ - ስራ ተቀባይነት የሚኖረው ተከታዮቹ ሁለት ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ነው፦
1- ለላቀው አላህ ተብሎ የተሰራ ከሆነ (ኢኽላስ)
2- እና በነብዩ ﷺ ሱና ከሆነ ነው (ሙታበዓ)

መልስ - ተገቢውን ሰበብ ከማድረስ ጋር ጥቅሞችን ለማምጣት እና ጉዳትን ለመመከት በላቀው አላህ ላይ መመካት ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {በአላህም ላይ የሚጠጋ ሰው እርሱ በቂው ነው።...} [ሱረቱ ጦላቅ፡ 3]
{حَسْبُهُ} ማለት ሌላ ሳያስፈልገው በቂው ነው ማለት ነው።

መልስ- አል-መዕሩፍ (መልካም) የሚባለው፡- አላህን እንዲታዘዙ መምከር ሲሆን፤ አል-ሙንከር የሚባለው ደግሞ አላህን ከማመፅ እንዲታቀቡ መገሰጽ ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ለሰዎች ከተገለጸች ሕዝብ ሁሉ በላጭ ሆናችሁ በጽድቅ ነገር ታዛላችሁ፤ ከመጥፎም ነገር ትከለክላላችሁ፤ በአላህም (አንድነት) ታምናላችሁ።...} [ሱረቱ ኣሊ-ዒምራን፡ 110]

መልስ - አህሉ ሱና ወልጀማዓህ የሚባሉት ከንግግርም፣ ከተግባርም ይሁን ከእምነት አኳያ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እና ባልደረቦቻቸው በነበሩበት አቋም ላይ የሆኑት ናቸው።
አህለ አስ-ሱንናህ የተባሉት፡ የነቢዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሱንና አጥብቀው በመከተላቸው እና ቢድዓን በመራቃቸው ሲሆን፤
ወልጀማዓህ የተባሉት ደግሞ:
በእውነት ላይ አንድ ዓይነት አቋም ስላላቸውና በዛም ያልተለያዩ በመሆናቸው ነው።