የልዩ ልዩ ክፍል

መልስ-
1 - ዋጂብ (ግዴታ)
2- ሙስተሐብ (የተወደደ)
3- ሐራም (ፈፅሞ የተከለከለ)
4- መክሩህ (የተጠላ)
5- ሙባሕ (የተፈቀደ)

መልስ-
1- ግዴታ (ዋጂብ)፡- አምስቱ የግዴታ ሰላቶች፣ የረመዳን ፆም እና ወላጆችን ማክበርን ይመስል፤
ዋጂብ (ግዴታ) ማለት አድራጊው መልካም ምንዳ የሚያገኝበት ሲሆን የተወው ደግሞ ቅጣት ይጠብቀዋል።
2- ሙስተሐብ (የሚወደድ)፡- ከግዴታ ሶላት በኋላ የሚሰገዱ ሱናዎች፣ የሌሊት ሶላት፣ ሚስኪን ማብላት እና ሰላምታ መለዋወጥ መሰል ነገራቶችን ሲሆን አንዳንዴም "ሱና" ወይም "መንዱብ" ይባላል።
- ሙስተሓብ የሚባለው ቢሰሩት አጅር የሚያስገኝ ቢተውት የማያስቀጣ ነው።
ጠቃሚ (አንገብጋቢ) ማስታወሻ፡-
አንድ ሙስሊም የሆነ ጉዳይ ሱና ወይም ሙስተሐብ መሆኑን ሲሰማ ተግባራዊ ለማድረግና የነብዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ፈለግ ለመከተል መጣደፍ ነው ይገባዋል።
3- ሙሐረም (የተከለከለ)፡- አልኮል መጠጣት፣ ወላጆችን ማመፅና ዝምድና መቁረጥን መሰል ተግባራቶችን ነው።
ሙሐረም የሆነ ነገር የተወ ሰው ምንዳ የሚያገኝበት የሰራ ደግሞ የሚቀጣበት ነው።
4- መኩሩህ (የተጠላ)፡- በግራ እጅ መስጠትና መቀበል፣ በሶላት ወቅት ልብስን (ክርን ላይ) መሰብሰብን ይመስል
- መክሩህ ነገርን መተው መልካም ምንዳን ያስገኛል፤ የሠራ ሰው ግን አይቀጣም።
5- ሙባሕ (የተፈቀደ)፡ ፖም እንደመብላትና ሻይ እንደመጠጣት አይነቱ ሲሆን "ሐላል" ወይ "ጃኢዝ" ይባላል።
- ሙባሕ ስላደረጉት ምናዳ አያሰጥም፤ ስላላደርጉት አያስቀጣም።

መልስ - በመሰረቱ ሁሉም ሽያጭ እና ግብይቶች የላቀው አላህ ከከለከላቸው አንዳንድ ዓይነቶች በስተቀር የተፈቀዱ ናቸው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {መሸጥን አላህ ፈቅዷል። አራጣንም እርም አድርጓል።} [ሱረቱል በቀራህ 275]

መልስ-
1- ማጭበርበር: ለምሳሌ የሸቀጥን ነውር መደበቅ፤
የማጭበርበር ክልከልነትን በተመለከተ የአላህ መልእክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በአንድ የእህል ክምር -ማለትም የምግብ ክምር- በኩል እያለፉ ሳሉ እጃቸውን ወደ እህሉ ከተቱና ጣቶቻቸው አንዳች እርጥበት ሲያገኘው እንዲህ አሉ፡- “የእህሉ ባለቤት ሆይ! ይህ ምንድን ነው ይሄ?” እርሱም፡- "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ዝናብ መትቶት እኮ ነው" አላቸው። እርሳቸውም እንዲህ አሉት፦ "(የእርጥብ ክፍሉን) ሰዎች እንዲያዩት ከክምሩ በላይ በኩል ለምን አላስቀመጥከውም? የሚያጭበረብር ከኛ አይደለም።" ሙስሊም ዘግበውታል።
2- አራጣ፡- ለምሳሌ ከሆነ ሰው አንድ ሺህ ተቀብሎ ሲመልስለት ግን ሁለት ሺህ አድርጎ መመለስ ነው።
በእዳው ላይ የተጣለው ጭማሪ አራጣ ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {መሸጥን አላህ ፈቅዷል። አራጣንም እርም አድርጓል።} [ሱረቱል በቀራህ 275]
3- አልገረር ወ አልጀሃላህ፡- ይህ ሲባል በበግ (በፍየል) ጡት ውስጥ ያለን ወተት አልያም ሳይታደን በባህር ውስጥ ያለን አሳ መሸጥ የመሳሰሉትን የሚያካትት ነው።
በሐዲሥ እንደመጣው፡ (የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "የገረር" ሽያጭን ከልክለዋል።) ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ-1- የእስልምና ፀጋ፤ ከከሃዲያን አለመሆንህ፤
2- የሱና ፀጋ፤ ከቢድዓ ሰዎች አለመሆንህ፤
3-የጤንነት ፀጋ፤ በመስማትም፣ በማየትም፣ በመራመድም በሌላውም ሁሉ ጤናማ መሆን፤
4- የመብላት፣ የመጠጣትና የመልበስ ፀጋ፤
ሌሎችም የዋለልን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ፀጋዎችም ሁሉ።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {የአላህንም ጸጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም። አላህ በእርግጥ መሓሪ አዛኝ ነውና።} [ሱረቱ-ነሕል፡18]

መልስ- ያለብን ግዴታ፡- እርሱ ብቸኛ ፀጋ የሚውል በመሆኑ እርሱን በአንደበት ማመስገንና ማወደስ እነዚህን ፀጋዎች ደግሞ አላህ በሚታመፅበት ሳይሆን እርሱን በሚያስደስት ሁኔታ ማዋል ነው።

መልስ - ኢድ አልፈጥር እና ኢድ አል-አድሓ (አረፋ)
አነስ ባስተላለፈው ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ወደ መዲና በመጡ ጊዜ ሰዎቹ በደስታ የሚያሳልፏቸው ሁለት ቀናት ነበሯቸው። እርሳቸውም (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን)፡- "እነዚህ ሁለት ቀናት ምንድን ናቸው?" ብለው ጠየቁ፡ ሰዎቹም፡- "እኛ በቅድመ-ኢስላም የነበሩን የደስታ ቀናት ናቸው።" ብለው መለሱ። እርሳቸውም (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን)፦ "አላህ ከእነርሱ የተሻሉ በሆኑ ሁለት በዓላት ማለትም በዒድ አልፈጥር እና በዒድ አል-አድሓ ለውጦላችኋል።" አቡ ዳውድ ዘግበውታል።
ከእነዚህ ውጭ ያሉት በዓላት ቢድዓ ናቸው።

መልስ - የረመዳን ወር ነው።

መልስ - ጁሙዓህ ቀን ነው።

መልስ- ለይለቱል ቀድር ነው።

መልስ፡- ግዴታው እይታን ዝቅ ማድረግ ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፡- {ለምእመናን ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን (ያልተፈቀደን ከማየት) ይከልክሉ።} [ሱረቱ-ኑር፡ 30]

1- በክፋት የምታዝ ነፍስ፡- ይህም የላቀው አላህን በማመፅ በኩል የሰው ልጅ ነፍሱንና ስሜቱ ያዘዘችውን ነገር መከተሉ ነው። ጥራት ይገባውና፡ {ነፍስ ሁሉ ጌታዬ የጠበቃት ካልሆነች በስተቀር በመጥፎ ነገር በእርግጥ አዛዥ ናትና። ጌታዬ በጣም መሓሪ አዛኝ ነው» (አለ)።} [ሱረቱ ዩሱፍ፡ 53] 2- ሸይጧን፡- የሰው ልጅን ማጥመምና በክፋት ወስውሶ እሳት የማስገባት ዓላማ ያለው የሰው ልጆች ጠላት ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፡- {የሰይጣንንም እርምጃዎች አትከታተሉ። እርሱ ለእናንተ ግልጽ ጠላት ነውና።} [ሱረቱል በቀራህ 168] 3- መጥፎ ጓደኞች፡- ክፋትን የሚያበረታቱና ከመልካም የሚከለክሉት ናቸው። አላህ እንዲህ ብሏል፡- {ወዳጆች በዚያ ቀን ከፊላቸው ለከፊሉ ጠላት ነው። አላህን ፈሪዎች ብቻ ሲቀሩ።} [ሱረቱ ዙኽሩፍ፡ 67]

መልስ- ተውባ ማለት፡- የላቀው አላህን ከማመፅ እርሱን ወደመታዘዝ መመለስ ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፡- {እኔም ለተጸጸተ፣ ላመነም፣ መልካምንም ለሠራ፣ ከዚያም ለተመራ ሰው በእርግጥ መሓሪ ነኝ።} [ሱረቱ ጠሃ፡ 82]

መልስ- 1- ከኋጢአት መታቀብ፤
2 - ስላለፈው ነገር መጸጸት፤
3- ወደ ኋጢአቱ ላለመመለስ መወሰን፤
4- የሰዎችን ሐቅ መመለስና የበደልናቸውም ካለ ይቅርታቸውን መጠየቅ።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ለእነዚያም መጥፎ ሥራን በሠሩ ወይም ነፍሶቻቸውን በበደሉ ጊዜ አላህን የሚያስታውሱና ለኀጢአቶቻቸው ምሕረትን የሚለምኑ ለሆኑት ከአላህም ሌላ ኀጢአቶችን የሚምር አንድም የለ። (በስሕተት) በሠሩትም ላይ እነርሱ የሚያውቁ ሲሆኑ የማይዘወትሩ ለሆኑት (ተደግሳለች)።} [ሱረቱ ኣል ዒምራን፡ 135]

መልስ - ነብዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) የላቀው አላህ በላይኛው ቀበሌ እንዲያወድሳቸው አላህን መማፀን ማለት ነው።

መልስ - "ሱብሐነላህ" ማለት የላቀው አላህ ከእንከን፣ ከስህተትና ከመጥፎ ነገር ሁሉ ማጥራት ማለት ነው።

መልስ - የላቀው አላህን ማመስገንና እርሱንም በሁሉም የፍጹምነት ባህሪያት መግለፅ ነው።

መልስ- ማለት ጥራት የተገባው አምላካችን አላህ ከሁሉም በላይ፣ ይበልጥ ታላቅ፣ ልዑልና ሁሉንም አሸናፊ ነው ማለት ነው።

መልስ - ትርጉሙ፡- በአላህ ካልሆነ በቀር ባርያው ከአንዱ ሁኔታ ወደ ሌላ የሚለወጥበት ብልሀትም ይሁን በዚሁ ላይ ችሎታም የለውም።

መልስ - ማለትም፡- ባሪያው አላህ ኃጢአቱን እንዲሰርዝለትና ጥፋቱን እንዲሸፍንለት ጌታውን መማፀኑ ነው።