የዱዓእ እና አዝካር ክፍል

ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "አላህን የሚያስታውስና አላህን የማያስታውስ ሰው ምሳሌው እንደ ህያዋንና ሙታን ነው።" ቡኻሪይ ዘግበውታል።
- ይህም የሆነበት ምክንያት የሰው ልጅ የህይወት ዋጋ የላቀው አላህን በማስታወሱ ልክ የሚተመን በመሆኑ ነው።

መልስ-1- አርረሕማንን ያስደስታል፤
2- ሸይጣንን ያባርራል፤
3- ሙስሊምን ከመጥፎ ነገር ይጠብቀዋል፤
4- የአላህን ምንዳና ሽልማት ያስገኛል፤

መልስ- በላጩ ዚክር "ላ ኢላሃ ኢለላህ" ነው። ቲርሚዚይ እና ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል።

መልስ- "አልሐምዱ ሊላሂ አልለዚ አሕያና በዕደ ማ አማታና ወኢለይሂን-ኑሹር።" (ትርጉሙም: ከሞት በኋላ ህይወት ለሰጠን አላህ ምስጋና የተገባ ነው። መመለሻም ወደርሱው ነው።) ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ- "አልሐምዱ ሊላሂ አል-ለዚ ካሳኒ ሀዛ አስሠውበ ወረዘቀኒሂ ሚን ገይሪ ሐውሊን ሚኒ ወላ ቁዋህ።" (ትርጉሙም፡ የኔ አቅም ወይም ብልሀት ሳይታከልበት ይህንን (ልብስ) እንድለብስ ላደረገኝ አላህ ምስጋና ይገባው።) አቡ ዳውድ እና ቲርሚዚይ እንዲሁም ሌሎችም ዘግበውታል።

መልስ- "ቢስሚላህ" (ትርጉሙም: "በአላህ ስም") ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

መልስ- "አላሁምመ ለከል-ሐምዱ አንተ ከሰውተኒሂ፤ አስአሉከ ኸይርሂ ወኸይረ ማ ሱኒዐ ለሁ፤ ወአዑዙ ቢከ ሚን ሸሪሂ ወሸሪ ማ ሱነዑ ለህ" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ አልብሰሀኛልና ምስጋና ላንተ ይሁን። ከመልካምነቱና ከተሰራበት መልካም ነገር እጠይቅሃለሁ። ከክፋቱና ከተሰራበት ክፋትም ጥበቃህን እሻለሁ።} አቡ ዳውድ እና ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

መልስ - ሌላ ሰው አዲስ ልብስ ለብሶ ካየሀው እንዲህ በማለት ዱዓእ ታደርግለታለህ፡- "ቱብላ ወ ዩኽሊፉል-ላሁ ተዓላ።" (ትርጉሙም፡ ልብሱ አልቆ አላህ ይተካልህ።) አቡ ዳውድ ዘግበውታል።

መልስ- "አሏሁመ ኢኒ አዑዙ ቢከ ሚነል ኹቡሢ ወልኸባኢሥ" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! እኔ ከውንድና ከሴት ጂኒ ባንተው እጠበቃለሁ።) ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ- "ጉፍራነክ" (ትርጉሙም: "መሀርታህን ለግሰኝ") አቡ ዳውድ እና ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

መልስ- "ቢስሚላህ" (ትርጉሙም "በአላህ ስም") አቡ ዳውድና ሌሎችም ዘግበውታል።

"አሽሀዱ አን ላ ኢላሀ ኢለላሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ወአሽሀዱ አንነ ሙሐመደን ዐብዱሁ ወረሱሉህ" (ትርጉሙም፡ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ እንደሌለና ሙሐመድም መልእክተኛው እና ባሪያው መሆናቸውን እመስከራለሁ።) ሙስሊም ዘግበውታል።

"ቢስሚላሂ ተወከልቱ ዐለላሂ ወላ ሐውላ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ" (ትርጉሙም፡ በአላህ ስም፤ በአላህ ተመካሁ። በአላህ ካልሆነ በቀርም ምንም ሃይልም ብልሀትም የለም።) አቡ ዳውድ እና ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

"ቢስሚላሂ ወለጅና ወ ቢስሚላሂ ኸረጅና ወዐላ ረቢና ተወከልና" (ትርጉሙም፡ በአላህ ስም ገባን፤ በአላህም ስም ወጣን፤ የምንመካውም በአላህ ነው።) ከዚያም ቤተሰቡን ሰላምታ ይስጥ። አቡ ዳውድ ዘግበውታል።

መልስ - "አልላሁምመ ኢፍተሕሊ አብዋበ ረሕመቲክ" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! የምህረትህን በሮች ክፈትልኝ።) ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ - “አላሁምመ ኢኒ አስአሉከ ሚን ፈድሊክ” (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! ከችሮታህ እማፀንሀለሁ።) ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ - ልክ ሙአዚኑ እንደሚለው እልና "ሐያ ዐለ ሰላህ" እና "ሐያ ዐለል ፈላሕ" ሲል “ላ ሐውላ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ” እላለሁ። ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ - (በነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ላይ ሶለዋት አወርዳለሁ።) ሙስሊም ዘግበውታል። "አላሁምመ ረብበ ሐዚሂ አድዳዕወቲ አትታማህ፤ ወስ-ሶላቲ አል-ቃኢማህ፤ አቲ ሙሐመዲን አል-ወሲለተ ወልፈዲላህ፤ ወብዐሥሁ መቃመን መሕሙደን አልለዚ ወዐድተህ።" (ትርጉሙም፡ የዚህ የተሟላ ጥሪና የተቋቋመው ሶላት ጌታ አላህ ሆይ! (ነብዩ) ሙሐመድን "ወሲላ" እና "ፈዲላ" ለግሳቸው፤ ቃል በገባህላቸው በተከበረው ቦታም ቀስቅሳቸው።) ቡኻሪይ ዘግበውታል።
በአዛንና በኢቃማ መካከልም ዱዓ ታደርጋለህ፤ ምክንያቱም በዛ ሰአት የተደረገ ዱዓእ አይመለስምና።

መልስ-1- አያተል-ኩርሲይ እቀራለሁ፡- "አልላሁ ላ ኢላሃ ኢላ ሁወል ሓዩል ቀዩም ላ ታእኹዙሁ ሲነቱን ወላ ነውም፤ ለሁ ማ ፊሰማዋቲ ወማ ፊል አርዲ፤ መንዘለዚ የሽፈዑ ዒንደሁ ኢላ ቢኢዝኒህ፤ ያዕለሙ ማ በይነ አይዲሂም ወማ ኸልፈሁም፤ ወላ ዩሒጡነ ቢሸይኢን ሚን ዒልሚሂ ኢላ ቢማ ሻአ፤ ወሲዐ ኩርሲዩሁ ሰማዋቲ ወልአርድ፤ ወላ የኡዱሁ ሒፍዙሁማ ወሁወል ዓሊዩል ዓዚም።" {አላህ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም። ሕያው ራሱን ቻይ ነው። ማንገላጀትም እንቅልፍም አትይዘውም። በሰማያት ውስጥና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የርሱ ብቻ ነው። ያ እርሱ ዘንድ በፈቃዱ ቢሆን እንጅ የሚያማልድ ማነው? (ከፍጡሮች) በፊታቸው ያለውንና ከኋላቸው ያለውን ሁሉ ያውቃል። በሻውም ነገር እንጂ ከዕውቀቱ በምንም ነገር አያካብቡም (አያውቁም)። መንበሩ ሰማያትንና ምድርን ሰፋ። ጥበቃቸውም አያቅተውም። እርሱም የሁሉ በላይ ታላቅ ነው።} [ሱረቱል በቀራህ፡ 255] 2- እንደሚክተለውም (ሱረቱል ኢኽላስንና ሁለቱን ቁል አዑዙ) እቀራለሁ፡- በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው። {በል «እርሱ አላህ አንድ ነው። (1) አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው። (2) አልወለደም፤ አልተወለደምም። (3) ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም። (4)} ሦስት ጊዜ። በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው። {በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ። (1) ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት። (2) ከሌሊትም ክፋት ባጨለመ ጊዜ። (3) በተቋጠሩ (ክሮች) ላይ ተፊዎች ከሆኑት (ደጋሚ) ሴቶችም ክፋት። (4) ከምቀኛም ክፋት በተመቀኘ ጊዜ፤ (እጠበቃለሁ በል)(5)} ሦስት ጊዜ። በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው። {በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ። (1) የሰዎች ሁሉ ንጉሥ በሆነው። (2) የሰዎች አምላክ በሆነው። (3) ብቅ እልም ባይ ከሆነው ጎትጓች (ሰይጣን) ክፋት። (4) ከዚያ በሰዎች ልቦች ውስጥ የሚጎተጉት ከሆነው። (5) ከጋኔኖችም ከሰዎችም (ሰይጣናት እጠበቃለሁ በል)(6)} ሦስት ጊዜ። "አላሁመ አንተ ረቢ ላ ኢላሃ ኢላ አንተ ኸለቅተኒ ወአነ ዐብዱክ ወ አነ ዐላ አህዲከ ወዋዕዲከ መስተጣዕቱ አዑዙ ቢከ ሚን ሸሪ ሶናዕቱ አቡኡ ለከ ቢኒዕመቲከ ዐለየ ወአቡኡ ቢዘንቢ ፈግፊር ሊ ፈኢነሁ ላ የግፊሩዝ-ዙኑበ ኢላ አንት"
(ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ አንተ ጌታዬ ነህ ከአንተ በቀርም አምልኮ የሚገባው የለም። አንተው ፈጠርከኝ እኔም ባሪያህ ነኝ። ቃል ኪዳንህንና ለአንተ የገባሁትንም ቃል ለመጠበቅ የቻልኩትን ያህል እጥራለሁ። በኔ ላይ ባለህ ችሮታና ኃጢአቴንም የማምን በመሆኔ ከሰራሁት ክፋት በአንተው እጠበቃለሁ። ማረኝ ከአንተ በቀር ኃጢአትን የሚምር የለምና።) ቡኻሪይ ዘግበውታል።

መልስ - “አላህ ሆይ! በስምህ እንሞታለን ህያው እንሆናለን።” ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ- "ቢስሚላህ" (ትርጉሙም፦ "በአላህ ስም" ማለት ነው።)
መጀመሪያ ላይ ከረሳህ ደግሞ፡-
"ቢስሚላሂ ፊ አወሊሂ ወአኺሪህ።" (ትርጉሙም፡ ቢስሚላህ ለመጀመርያው ለመጨረሻውም።) አቡዳውድ እና ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

መልስ- "አልሓምዱ ሊላሂ አልለዚ አጥዓመኒ ሀዛ ወረዘቀኒ፤ ሚን ገይሪ ሐውሊን ሚኒ ወላ ቁወህ።" (ትርጉሙም፡ የኔ ሀይልም ብልሀትም ሳይኖር ይህንን ምግብ ለመገበኝና ለለገሰኝ አላህ ምስጋና ይገባው።) አቡ ዳውድ፣ ኢብኑ ማጃህ እና ሌሎችም ዘግበውታል።

"አላሁምመ ባሪክ ለሁም ፊማ ረዘቅተሁም፤ ወግ’ፊር ለሁም ወርሐምሁም።" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! በሰጠሃቸው ነገር በረካ አድርግላቸው። ይቅር በላቸው እዘንላቸውም።) ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ- "አልሐምዱ ሊላህ"
ያኔ ወንድሙ ወይም ባልንጀራው “የርሐሙከላህ” (አላህ ይዘንልህ) ይበለው።
እንዲህ ካሉት እርሱም፦ "የህዲኩሙላሁ ወ ዩስሊሕ ባላኩም" ብሎ ይመልስ። ቡኻሪይ ዘግበውታል።

መልስ - "ሱብሐነከላሁመ ወቢሐምዲከ አሽሀዱ አን ላ ኢላሃ ኢላ አንተ አስተግፊሩከ ወአቱቡ ኢለይክ።" (ትርጉሙም: ክብርና ምስጋና ላንተ ይሁን፤ ከአንተ በቀር ሌላ አምላክ እንደሌለም እመሰክራ ለሁ፤ መሀርታህንም እከጅላለሁ ወደ አንተም ተፀፅቼ እመለሳለሁ።) አቡዳውድ እና ቲርሚዚይ እንዲሁም ሌሎችም ዘግበውታል።

መልስ- "ቢስሚላህ፤ ወልሐምዱሊላህ፤ ሱብሐነ አልለዚ ሰኸረ ለና ሀዛ ወማ ኩና ለሁ መቅሪኒን (13) ወኢና ኢላ ረቢና ለሙንቀሊቡን (14)" (አልሐምዱሊላህ፤ አልሐምዱሊላህ፤ አልሐምዱሊላህ፤ አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ሱብሐነከላሁምመ ኢኒ ዘለምቱ ነፍሲ ፈግፊርሊ ፈኢነሁ ላየግፊሩ ዙኑበ ኢላ አንት።" (ትርጉሙም፡ «ያ ይህንን የማንችለው ስንሆን ለእኛ ያገራለን ጌታ ጥራት ይገባው። (13) እኛም በእርግጥ ወደ ጌታችን ተመላሾች፤ነን 14» ምስጋና ለአላህ ይገባው። ምስጋና ለአላህ ይገባው። ምስጋና ለአላህ ይገባው። አላህ ታላቅ ነው። አላህ ታላቅ ነው። አላህ ታላቅ ነው። አላህ ሆይ! ጥራት ይገባህ ነፍሴን በድያለሁ። ማረኝ ከአንተ በቀር ኃጢአትን የሚምር የለምና።) አቡዳውድ እና ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

መልስ- "አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ {ሱብሐነ አልለዚ ሰኸረ ለና ሀዛ ወማ ኩና ለሁ መቅሪኒን (13) ወኢና ኢላ ረቢና ለሙንቀሊቡን (14)} አልላሁመ ኢንና ነስአሉከ ፊ ሰፈሪና ሀዛ አል-ቢረ ወት-ተቅዋ ወሚነል ዐመሊ ማ ተርዷ አላሁመ ሀውዊን ዐለይና ሰፈሪና ሀዛ ወጥዊ ዓና ባዕደሁ አላሁመ አንታስ-ሷሒቡ ፊስ-ሰፈር ወል-ኸሊፈቱ ፊል-አህሊ አላሁመ ኢንኒ አዑዙ ቢከ ሚን ወዕሣኢ-ሰፈር ወካአባቲል-መንዞር ወሱኢል-ሙንቀለቢ ፊል-ማሊ ወል-አህል" (ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው። አላህ ታላቅ ነው። አላህ ታላቅ ነው። «ያ ይህንን የማንችለው ስንሆን ለእኛ ያገራለን ጌታ ጥራት ይገባው። (13) እኛም በእርግጥ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን (14)» አላህ ሆይ! በዚህ ጉዟችን ለበጎነት እና ለመልካምነት አንተንም ለሚያስደስቱን ተግባሮች እንድትገጥመን እንማፀንሃለን። አላህ ሆይ! ይህን ጉዞ አቅልልን እና ርቀቱንም ቅርብ አድርግልን። አላህ ሆይ! በመንገዳችን ያለሀን ረዳታችን እና ለቤተሰቦቻችንም የተውንላቸው አንተን ነው። አላህ ሆይ! ከጉዞ መከራና ከክፉ እይታዎችም ባንተ እጠበቃለሁ። በቤተሰባችንና በንብረታችን ስንመለስ በችግር ውስጥ ከማግኘትም ባንተው እንጠበቃለን።)
ተመልሶም ሲመጣም እንዲሁ ካለ በኋላ ተከታዩንም ያክላል፦
"ኣይቡነ፤ ታኢቡነ፤ ዓቢዱን ሊረቢና ሐሚዱን" (ትርጉሙም፡ ጌታችንን እያመሰገንን ተፀፃቾችና፤ ተውባ አድራጊዎች፤ ለጌታችን አመስጋኞች ሆነን ተመለስን።) ሙስሊም ዘግበውታል።

"አስተውዲዑኩሙላሁ-ል-ለዚ ላ ቱደዪዑ ወዳኢዑሁ" (ትርጉሙም፡ አደራየን እርሱ ዘንድ የተጣለ አደራ በማይጠፋው አላህ ላይ አድርጌ እሰናበትሀለሁ።) ኢማም አሕመድ እና ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል።

"አስታውዲኡላሀ ዲነክ፤ ወ አማነተክ፤ ወ ኸዋቲመ ዐመሊክ።" (ትርጉሙም፡ ሀይማኖትህን፣ ደህንነትህንና የሥራ ፍፃሜህን በአላህ ላይ አደራ እተወዋለሁ።) ኢማሙ አሕመድና ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

"ላ ኢላሀ ኢለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፡ ለሁል-ሙልኩ ወለሁል-ሐምዱ ዩሕይ ወዩሚት፤ ወሁወ ሐዩን ላ የሙት፤ ቢየዲሂል-ኸይር ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር።" (ትርጉሙም፡ ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ ተጋሪ የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። ሕያው ያደርጋል፤ ይገድላልም። እርሱም የማይሞት ሕያው ነው። መልካም ሁሉ በእጁ ነው እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።) ቲርሚዚይ እና ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል።

መልስ- "አዑዙ ቢላሂ ሚነሽሸይጧን አርረጂም" (ትርጉሙ፡ ከተረገመው ሸይጣን በአላህ እጠበቃለሁ።) ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

መልስ- "ጀዛከላሁ ኸይረን" (ትርጉሙም፡ መልካም ምንዳህን አላህ ይክፈልህ።) ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

መልስ- "ቢስሚላህ" (ትርጉሙም፦ "በአላህ ስም" ማለት ነው።) አቡዳውድ ዘግበውታል።

መልስ- "አልሐምዱ ሊላሂ አልለዚ ቢኒዕመቲሂ ተቲሙ አስሷሊሓት" (ትርጉሙም፡ ያ በጎዎችም በጸጋው የሚሞሉት አላህ ምስጋና መላ ተገባው።) አል-ሐኪም እና ሌሎችም ዘግበውታል።

መልስ- "አልሐምዱ ሊላህ ዐላ ኩሊ ሐል" (ትርጉሙም፡ በሁሉም ሁኔታ ምስጋና ሁሉ ለአላህ የተገባ ነው።) ሰሒሑል ጃሚዕ ላይ ተዘግቧል።

መልስ- ሙስሊም እንዲህ ነው ሰላምታ የሚያቀርበው፡ "አሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላሂ ወበረካቱህ" (ትርጉሙም፡ የአላህ ሰላም፣ እዝነትና በረከቱ በርሶ ላይ ይስፈን)
ለወንድሙም እንዲህ ሲል መለስ ይሰጣል፦ "ወዐለይኩም አስሰላም ወረሕመቱላሂ ወበረካቱህ" (ትርጉሙም፡ በእርሶም ላይ የአላህ ሰላም፣ እዝነትና በረከቱ ይስፈን) ቲርሚዚይ እና አቡ ዳውድ እንዲሁም ሌሎችም ዘግበውታል።

መልስ- "አሏሁመ ሶይበን ናፊዐን" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! መልካም ቧቧታ አድርገው።) ቡኻሪይ ዘግበውታል።

መልስ- "ሙጢርና ቢፈድሊላሂ ወረሕመቲሂ" (ትርጉሙም፡ በአላህ እዝነትና ችሮታ ዝናብ አገኘን።) ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።

"አልላሁመ ኢኒ አስአሉከ ኸይረሀ ወአዑዙ ቢከ ሚን ሸሪሃ" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! እኔ ኸይሯን እማፀንሃለሁ፤ ከክፋቷም በአንተው እጠበቃለሁ።) አቡ ዳውድ እና ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል።

"ሱብሐነለዚ ዩሰቢሑ ረዕዱ ቢሐምዲሂ ወልመላኢከቱ ሚን ኺፈቲሂ" (ትርጉሙም፡ ነጎድጓድም እያመሰገነ መላእክትም እርሱን ፈርተው የሚያወድሱት አላህ ጥራት ይገባው።) የኢማሙ ማሊክ ሙወጧእ ላይ ተዘግቧል።

"አልሐምዱ ሊላሂ አልለዚ ዐፋኒ ሚማ ኢብተላከ ቢሂ፤ ወፈደለኒ ዐላ ከሢረን ሚመን ኸለቀ ተፍዲላ" (ትርጉሙም፡ በአንተ ላይ ካደረሰብህ ፈተና ያተረፈኝ አላህ ምስጋና ይገባው፤ ከብዙሀኑ ፍጡራኑም በርግጥ አስበለጠኝ።) ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

መልስ- በሐዲሥ፡- ‹‹ከእናንተ አንዳችሁ ከወንድሙ ወይም ከራሱ፣ ወይም ከገንዘቡ የሚወደድ ነገርን የተመለከተ (አላህ በረካ እንዲያደርግለት ዱዓእ ያድርግ) የሰው ዓይን በትክክል ያለ ነገር ነውና።" ኢማም አሕመድ እና ኢብኑ ማጃህ እንዲሁም ሌሎችም ዘግበውታል።

መልስ- "አላሁመ ሰሊ ዐላ ሙሐመዲን ወዓላ ኣሊ ሙሐመዲን ከማ ሰለይተ ዐላ ኢብራሂም ወዐላ ኣሊ ኢብራሂም ወባሪክ ዓለ ሙሐመዲን ወዐላ አሊ ሙሐመዲን ከማ ባራክተ ዐላ ኢብራሂም ወዐላ ኣሊ ኢብራሂመ ኢነከ ሐሚዱን-መጂድ።" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! ሶለዋትህን በሙሐመድና በሙሐመድ ቤተሰብ ላይም አድርግ፤ ልክ በኢብራሂም እና በኢብራሂም ቤተሰቦች ሶለዋት እንዳደርግከው፤ አንተ ምስጉን የተከበርክ ነህና። አላህ ሆይ! በረከትህንም በሙሐመድ እና በመሐመድ ቤተሰቦች ላይም አድርግ ልክ በኢብራሂምና በኢብራሂም ቤተሰቦች እንዳደረግከው፤ አንተ ምስጉን የተከበርክ ነህና።) ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።